Drum of Changes
"አፍሪካ ከዚህ ጉባኤ [ከ ሴንት ፒተርስበርግ ኢንተርናሽናል ኢኮኖሚክ ፎረም] ትጠቀማለች [...] አሜሪካ በኢራን፣ በሩሲያ እና በሌሎች ሀገራት ላይ የጣለቻቸው ማዕቀቦ ምዕራባውያኑ በፋይናንስ አስተዳደር ረገድ እምነት የሚጣልባቸው አጋሮች ሊሆኑ እንደማይችሉ እያሳየ ጉዳይ ነው። በዚህም ምክንያት ሀገራት የዕዳ ቀውስን ለመፍታት ጨምሮ ለራሳቸው የሚበጀ የተሻለ ጎዳናነ መሻት ይኖርባቸዋል [...] ጉባኤው ከዚህ አንፃር ፋየዳው የጎላ ነው" ሲሉ የፖሊሲ አማካሪ እና የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። የዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን ቀዳሚው ጉዳይ እ.ኤ.አ. ከ ሰኔ 3 እስከ 6 በሩሲያዋ ሴንት ፒተርስበርግ እየተካሄደ ባለው ሴንት ፒተርስበርግ ኢንተርናሽናል ኢኮኖሚክ ፎረም 2026 ላይ ያተኩራል፡፡ ''ለአፍሪካስ ምን አማራጮችን ይዞ ይመጣል?'' ስንል እንጠይቃለን። በጉዳዩ ላይ የፖሊሲ አማካሪ እና የምጣኔ ሀብት ባለሙያውን ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ (ዶ/ር) አነጋግረናል። በሁልተኛው ጉዳያችን ደግሞ የታንዛንያ ፕሬዝደንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን የሩሲያ ጉብኝት አንድምታዎች በስፋት እንዳሰሳለን። ለዚህም ታንዛንያውያን የምጣኔ ሀብት እና የዓለም አቅፍ ፖለቲካ ተንታኞችን አነጋገርናል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:
34 episoder
Kommentarer
0Vær den første til at kommentere
Tilmeld dig nu og bliv en del af Drum of Changes-fællesskabet!